ቤትዎ ቁጭ ብለው የሚሰሩት ስራ መጣልዎ! እንዴት ከታች ምስሉን ተጫኑ

Monday 19 November 2018

ሰኞ ምሽት የወጡ በርካታ አዳዲስ የዝውውር ዜናዎች

ማንቸስተር ዩናይትዶች የንጎሎ ካንቴ ወኪል ጋር ቀርበው ንግግር ጀምረዋል። ተጭዋቹን ሳይጠበቅ በጥር የዝውውር መስኮት ላይ ወደ ኦልትራፎርድ። ለማዛወር ወጥነዋል።  (ምንጮች፦ M.E.N,Star እና Express)



የሊቨርፑሉ አለቃ የርገን ክሎፕ አሜሪካዊውን የዶርትመንድ አማካይ ክርስቲያን ፑሊሲች በ £70 ሚሊዮን የዝውውር ዋጋ ለማዛወር በሚደረገው ፉክክር ላይ ቼልሲን ተቀላቅለዋል።  (ምንጭ፦ Sunday Mirror)



የአርሰናሉ አማካይ አሮን ራምሴይ ወደ ጁቬንቱስ ለመዛወር የሚስማማ ከሆነ አመታዊ የ£10.4 ሚሊዮን ደሞዝ ሊከፍሉት ፈቅደዋል።  (ምንጭ፦ Sun on Sunday)



ካስካሪኖ : “ምን አለ በሉኝ! ጎሜዝ ለቀጣዩ አስር አመታት የእንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን ቀዳሚው ተመራጭ መሃል ተከላካይ ይሆናል። አሰልጣኙ ቡድኑን በሚመርጥበት ግዜ በቀዳሚነት የሚያስቀምጠው እርሱን ይሆናል" - ሲል ተጭዋቹ ከፊቱ ብሩህ ተስፋ እንዳለው መስክሮአል።
(ምንጭ፦ liverpoolfc)



ጂኒ ዊናልድረም: “ሰዎች ብዙ ግዜ እኔ የአማካይ ስፍራ ተጭዋች እንዳልሆንኩ ይልቅ የክንፍ መስመር ተጭዋች እንደሆንኩ ሊነግሩኝ ይፈልጋሉ።"

"በርካታ አሰልጣኞች 'በክንፍ መስመር ላይ ብትጫወት ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግህ ልዩ ክህሎት አለህ' እያሉ የሚመክሩኝ አሰልጣኞች ብዙ አሉ" - ሲል የርገን ክሎፕ በክንፍ መስመር እንዲሞክሩት እግረ መንገዱን ጠቁሟል።
(ምንጭ፦ liverpoolfc)



ማንቸስተር ዩናይትዶች የዌስትሃሙን ዲክላን ሪሴ ለማዛወር ሙከራ ላይ ናቸው ሆኖም ለተጭዋቹ ዝውውር ከአርሰናል እና ሊቨርፑል ፉክክር ገጥሞአቸዋል።  (Source: Daily Express)



ሪያል ማድሪዶች በጥር የዝውውር መስኮት ላይ አጥቂ ለማዛወር ወደ ገበያው ይወጣሉ። ሉስ ብላንኮዎቹ በጋሬዝ ቤል እና ካሪም ቤንዜማ ላይ የነበራቸው እምነት ተሟጧል።  (Source: Sport)



ማንቸስተር ዩናይትዶች የሮማውን ሎሬንዞ ፔሌግሪኒ ደሞዝ እጥፍ በማድረግ ለማዛወር ሙከራ እያደረጉ ነው። ተጭዋቹ በ£26 ሚሊዮን የዝውውር ሂሳብ ወደ ኦልትራፎርድ ሊያመራ ይችላል የሚሉ ዘገቦች ተበራክተዋል።  (ምንጭ፦ Corriere dello Sport)



ኤሲ ሚላኖች ስፔናዊውን የቼልሲ አማካይ ሴስክ ፋቤጋዝ በጥር የዝውውር መስኮት ላይ ስለሚያዛውሩበት ሁኔታ ከወዲሁ ንግግር ማድረግ ጀምረዋል።   (ምንጭ፦ Calciomercato)



ሪስ ኔልሰን ሆፌንሄምን በውሰት ለመቀላቀል ስለመወሰኑ: “እኔ ሁሌም ያለኝን አቅም በማውጣት ምርጥ ተጭዋች የመሆን ህልም አለኝ። ገና 18 አመቴ ላይ ብሆንም ወደ ቡንደስሊጋው ብዛወር ጥሩ ፈተና ሊሆነኝ እንደሚችል አውቃለሁ። ወደዛ መዛወሬ የተሻልኩ ተጭዋች እንደሙያደርገኝ አምን ነበር። ወደ ጀርመን መሄዴ በቀጣይ የእግርኳስ ህይወቴም ከሜዳም ውጪ እንደሰው የተሻልኩ እንደምሆን ተስፋዬ ነው።"



ናፖሊዎች ምንም እንኳን በውሰት ያዛወሩት ግብ ጠባቂያቸው ዴቪድ ኦስፒና ውሉ ላይ እንደሰፈረው 'በ30 ጨዋታዎች ላይ ሆኖ ከተሰለፈ ዝውውሩ ቋሚ ይሆናል' የሚለው አንቀፅ ሳያስገድዳቸው ግብ ጠባቂውን በክረምት ሊያስፈርሙት ከውሳኔ ላይ ደርሰዋል።   (ምንጭ፦ La Repubblica)



ሮበርት ሎዋንዶውስኪ በዚህ የውድድር አመት በሁሉም ውድድሮች ላይ ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች ላይ ያስመዘገበው የጎል መጠን 15 ሲሆን 5 ጎል የሆኑ ኳሶችን አቀብላል። በየ72 ደቂቃ አንድ ጎል ላይ በማግባት አሊያም በማቀበል ተሳትፎ አድርጎአል።
(ምንጭ፦ iMiaSanMia)



በበርካታ ታላላቅ ክለቦች አይን ውስጥ የገባው ሆላንዳዊ አማካይ ማቲያስ ዲ ሊዥት ሆላንድ እና ጀርመን ጨዋታ ወቅት ጋዜጣዊ መግለጫ በሚሰትበት ወቅት ባየር ሚኒኮች ሊያስፈርሙት ጥያቄ ስለማቅረባቸው ቢጠይቁትም የሆላንድ ቡድን ፕሬስ ኦፊሰር የሆኑት ግለሰብ ግን መልስ እንዲሰጥ አልፈቀዱለትም፤ ምክንያቱም ጋዜጣዊ መግለጫው የዝውውር ሁኔታ ቃለ ምልልስ አይደለም ብለዋል።
(ምንጭ፦ Kicker)



ባየር ሙኒኮች በቀጣይ ክረምት የዝውውር መስኮት ላይ ቡድናቸውን በአዲስ ስብስብ ለማጠናከር ያቀዱ ሲሆን ሁለት የክንፍ መስመር ተጭዋቾችን ለማዛወር አቅደዋል።  (ምንጭ፦ Kicker)



የፖርቹጋል ብሄራዊ ቡድን ካምፕ እንዳረጋገጠው ከሆነ የማን.ሲቲው በርናንዶ ሲልቫ የአካል ብቃት ችግር ስላለበት ዛሬ ከቡድኑ ጋር ልምምድ አላደረገም። ቡድኑ ነገ ከፖላንድ ጋር በሚያደርገው የUNL ጨዋታ ላይም አይሰለፍም።  (ምንጭ፦ CityWatch)



ሪያል ማድሪዶች የ21 አመቱን የአያክስ አማካይ ፍራንክ ዲ ጆንግ ለማዛወር በሚደረገው ፉክክር ላይ ዘግይተውም ቢሆን ተቀላቅለዋል። ሆኖም የረፈደባቸው ይመስላል። የማን.ሲቲው ቲኪ ብምግሪስታን ለበርካታ ጊዜያት ያህል ከክለቡ አያክስ እና ከተጭዋቹ ጋር ተገናኝተው ዝውውሩ ላይ ከተፎካካሪዎቻቸው ቀድመው ተገኝተዋል። የባርሴሎናዎችም በተጭዋቹ ዝውውር ድርድሩ ላይ ቀደም በማለት ገፍተው የተንቀሳቀሱ ሌላኛው ክለብ ናቸው።  (ምንጭ፦ SPORT)



ኤሲ ሚላኖች በውሰት ከለንደኑ ክለብ ቼልሲ ያዛወሩትን አማካይ ቲሞው ባካዮኮ ውል ወደ ቄሚ ዝውውር ለመቀየር ፍላጎት ያሳደሩ ቢሆንም ለዝውውሩ ከ £22 ሚሊዮን በላይ ለሰማያዊዎቹ መክፈል አይፈልጉም።  (ምንጭ፦ 90min)



ሉዊስ ሄነሪኬ በዴቪድ ደ ሂያ ላይ ያላቸው እምነትና ትግስት በመሟጠጡ በእርሱ ምትክ የቼልሲውን ግብ ጠባቂ የስፔን ብሄራዊ ቡድን ቁጥር1 ተመራጭ ለማድረግ ከውሳኔ ላይ ደርሰዋል።  (ምንጭ፦ 90min)



ማንቸስተር ዩናይትዶች የናፖሊውን መሃል ተከላካይ ካሊዱ ኩሊባሊ ለማዛወር የ€90 ሚሊዮን ወይም £80 ሚሊዮን ሂሳብ ለክለቡ አቅርበዋል።
(ምንጭ፦ Metro)

No comments:

Post a Comment