ቤትዎ ቁጭ ብለው የሚሰሩት ስራ መጣልዎ! እንዴት ከታች ምስሉን ተጫኑ

Tuesday 20 November 2018

አርሰናል ቼልሲ እና ሊቨርፑልን የተመለከቱ ትኩስ የዝውውር ዜናዎች



ትልቅ ዜና ለቼልሲ ደጋፊዎች! ንጎሎ ካንቴ ከሰማያዊዎቹ ጋር የሚያቆየውን የክለቡን ሪከርድ አዲስ ኮንትራት ለመፈረም ተዘጋጅቷል ..

ንጎሎ ካንቴ በቼልሲ ያለውን ኮንትራት ማደስ እንደሚፈልግ ፍቃደኝነቱን ጠቁሟል። ቼልሲዎች በበኩላቸው ለፈረንሳዊው አማካይ የክለቡ ሪከርድ የሆነ ሳምንታዊ የ£290,000 ደሞዝ ሊከፍሉት እንደሚፈልጉ Goal ተረድቻለሁ በሚል ዘግቧል።

የ27 አመቱ ኮከብ በስታምፎርድ ብሪጁ ክለብ ደስተኛ ሲሆን ወደ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በ2015 ሌስተርን ተቀላቅሎ ከመጣ በኃላ ሊጉ ለርሱ አጨዋወት አመቺ ሆኖለታል።

ካንቴ አሁን በቼልሲ ሳምንታዊ £150,000 ደሞዝ የሚከፈለው ሲሆን ውሉ በ2021 የሚያበቃ ይሆናል። አማካዩ ክለቡ ቼልሲ ረጅም ኮንትራት ሊያስፈርማቸው ከሚፈልጋቸው ተጭዋቾች መሃል ከኤዲን ሃዛርድ ቀጥሎ ሁለተኛው ነው።


በሌላ ዜና የቦሩሲያ ዶርትመንዱ አማካይ ክሪስቲያን ፑሊሲች ቡንደስሊጋውን በመልቀቅ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ይመጣል። ሆኖም የቼልሲ እና የሊቨርፑል የዝውውር ኢላማ የሆነው ተጭዋች በጥር ሳይሆን በክረምቱ ዝውውር ወቅት ብቻ ዶርትመንድን እንደሚለቅ ተነግሯል። (ምንጭ: Daily Mirror)


GUNNING FORNALS አርሰናሎች ያለ አሮን ራምሴይ ህይወትን በኤምሬትስ ለማስቀጠል ተዘጋጅተዋል።

እናም ኡናይ ኤምሬ የቪያሪያሉን አማካይ ፓብሎ ፎርናሌስን ለማዛወርና የዌልሳዊው ምትክ ለማድረግ ተዘጋጅተዋል። ተጭዋቹ በዚህ አመት በላ ሊጋው ያገባት ጎል Goal Of The Season በሚል እጩ በመሆን ሊመረጥለት ችሏል።

አርሰናሎችም የስፔናዊው ተጭዋች ውል ማፍረሻ ሂሳብ የ£17.8 ሚሊዮን በመክፈል በጥር የዝውውር መስኮት ሊያስፈርሙት ተዘጋጅተዋል።

No comments:

Post a Comment