ቤትዎ ቁጭ ብለው የሚሰሩት ስራ መጣልዎ! እንዴት ከታች ምስሉን ተጫኑ

Wednesday 14 November 2018

ማርኮ አርናቶቪች ማን.ዩናይትድን በጥር ሊቀላቀል እንደሚችል ወኪሉ ፍንጭ ሰጠ

አርናቶቪች እንዳለው ከሆነ ዌስትሃምን በጥር የዝውውር መስኮት ላይ መልቀቅ ይፈልጋል።

አዉስትሪያዊዉ ኮከብ ከምርጥ ተጭዋቾች ጎን መጫወት እፈልልለሁ ያለ ሲሆን ወኪሉ እና ወንድሙ የሆነው ዳንዥል እንዳለው ከሆነ ቀጣይ ሊዛወር የሚፈልግበት ክለብ የተሻለ ትልቅ ቡድን ነው።


MARKO ARNAUTOVIC ክለቡን መልቀቅ እንደሚፈልግ በመናገር የክለቡን ደጋፊዎች አስደንግጧል።

የዌስትሃሙ አንበል ባለፈው ሲዝን ላይ የቡድኑ ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪ ሆኖ የጨረሰ ሲሆን ቡድኑ ወደ ታችኛው ዲቪዚዮን እንዳይወርድ ያድነናል ብለው ተፋ ያደረጉበት ተጭዋቻቸውም ነበር።

ሆኖም የቀድሞው የስቶክ ሲቲው ሰው ኮከብ በከፍተኛ ደረጃ መጫወት እፈልጋለሁ ብሏል። ወንድሙ እና ወኪሉ ዳንዥል ለአውስትሪያው ጋዜጣ Kurier እንዳለው ከሆነም ..

"አሁን ቀጣይ ክለብ ላይ ለመጫወት ተዘጋጅቷል።"

አርናቶቪች በበኩሉ ..
"አሁን የ29 አመት ሰው ነኝ። ይሄ ጥር እድሜዬ ነው።
ከምርጥ ተጭዋቾች ጋር መፎካከር ራሴን ማየት መፈለጌ ኖርማል ነው።

"ሆኖም በዚህ ጉዳይ ላይ ወንድሜን በጣም አምነዋለሁ።"

የአርናቶቪች ወንድም ተጭዋቹ በ2017 ላይ ከስቶክ ሲቲ ወደ መዶሻዎቹ በ£25 million የዝውውር ሂሳብ እንዲዛወር ያደረገ ወኪሉም ነው። እናም አሁንም ለተጭዋቹ ገዢ ክለብ ለመፈለግና ለመደራደር ቢዚ እንደሚሆን ይጠበቃል።

ለአውስትሪያው ጋዜጣ እንዳለው ከሆነ ..

"አሁን ተጭዋቹ በፕሪሚየር ሊጉ የመጫወት በቂ ልምድ አዳብሯል። ይሄ ሊግ ደሞ ምርጥ ተጭዋቾች የሚገኙበት ሊግ ነው። ሆኖም ማርኮን ለመሰለ ጎበዝ ተጭዋች ደግሞ በዌስትሃም ብቻ መጫወት ትልቁ ግብ አይደለም።

"የዌስትሃም ቡድን አንዱ ትልቁ አካል እንደሆነ ይታወቃል። ሆኖም የተሻለ ክለብ መቀየሩ የሚቻል ነገር ነው።

"ለትልቅ ክለብ መጫወት አለበት። ማርኮ ለቀጣይ ስቴፑ አሁን ዝግጁ ሆኑአል። እንደርሱ አይነት ተጫዋች ለመውረድ በሚታገል ቡድን ውስጥ መጫወት የለበትም። ከፍ ባሉ ደረጃዎች ባላቸው ውድድሮችም ላይ መሳተፍ አለበት።

"ማርኮ ለዌስትሃም መጫወቱን ወዶታል። ክለቡን።እና ደጋፊዎቹን ከልቡ ይወዳል።"

የማርኮ አርናቶቪች የእግርኳስ ህይወት ስታቶች..

• ለትዌንቴ ክለብ : 59 appearances - 14 goals
• ለኢንተር ሚላን : 3 appearances - 0 goals
• ለወርደር ብሬመን : 84 appearances - 16 goals
• ለስቶክ : 145 appearances - 26 goals
• ለዌስትሃም : 46 appearances - 16 goals

"በጥር ሊለቅ የሚችልበት አማራጮች አሉን። እንደውም በክረምቱ ክለቡን ለመልቀቅ በጣም በጣም ተቃርቦ ነበር"

ማንቸስተር ዩናይትዶች የ29 አመቱን ተጭዋች ያስፈርማሉ በሚል በክረምቱ በተደጋጋሚ ስማቸው ሲነሳ ቆይቷል። እናም አሁንም በድጋሚ በጥር ወር ፊርማውን ለማግኘት እንደሚንቀሳቀሱ ይጠበቃል።

No comments:

Post a Comment